የጃፓን አለማቀፍ ትብብር ድርጅትና የካይዘን የልዕቀት ማዕከል ከተለያዩ የፊደራል ሆስፒታሎች ጋር በመሆን የሆስፒታሉን የካይዘን አተገባበር ጉብኝት አድርገዋል፡፡ 

News Image
ታህሳስ3/2016 ዓ.ም የጃፓኑ አለማቀፍ ትብብር ድርጅት ከካይዘን የልዕቀት ማዕከል ጋር በጋር በመሆን በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሰራውን የካይዘን ትግበራ ተግባረዊ በሆነባቸው የሆስፒታሉ የስራ ክፍሎች፣ከጤና ሚኒስቴር ሜዲካል ሰርቪስ፣ከየካቲት 12 ሆስፒታልና ከቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተገኙ እንግዶች ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
በውይይቱና በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የሆስፒታሉ የጤና መረጃ ስርዓት ዳይሬክቶሬት አቶ ሃብታሙ ብርሃኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ሆስፒታሉ የካይዘን ትግበራውን በመጀመሩ በከፍተኛ ሁኔታ ለውጥ ያመጣበትና የማሻሻያ ስራዎችን በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ ትግበራው በተለያዩ የስራ ክፍሎች ተጠሪ ባለሙያ ተመድቦለት ስራው ተግባራዊ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ የካይዘን ትግበራው ተግባራዊ ከሆነባቸው የስራ ክፍሎች መካከል ደግሞ የህሙማን የመረጃ ክፍል፣የፋርማሴ አገልግሎትና ባዮሜዲካል ወርክ ሾፕ ክፍል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ካይዘን ለሆስፒታላችን እንደሲስተም በመተግበሩ ለተገልጋዩ ማህበረሰብ የሚታዩ ለውጦችን እያሳየ በመሆኑና የካይዘን አንዱ መግቢያችን የሆነውን የተገልጋዮችን የአገልግሎት መስጫ ቦታዎችን በትክክል ተግባራዊ በመደረጋቸው ሶስቱንም ካይዘን ተግባረዊ የሆነባቸውን ክፍሎች በጉልበትም ይሁን በገንዘብ የሚወጣውን ወጪ ማዳን መቻሉን አመስግነው በተጀመሩ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች ላይ ማስፋፋቱን የምንቀጥል ይሆናል ሲሉም ለእንግዶች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሆስፒታሉ ያለበትን የካይዘን የአፈፃፅም ደረጃና በተመረጡ የሆስፒታሉ ካይዘን ትግበራ በሚደረግባቸው የስራ ክፍሎችም የእውቅናና የምስክር ወረቀት ከጃፓን አለም አቀፍ ትብብርና ከካይዘን የልዕቀት ማዕከል የተሰጣቸው መሆኑንም ወ/ሮ የልፍኝ አማረ በሪፖርታቸው አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ሪፖርት ላይ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን አለርት ሆስፒታል የካይዘን ትግበራውን አዋጭና ቀጣይነት ያለው መሆኑን ተረድቶ ተግባራዊ በተደረገባቸው የስራ ክፍሎችም ሆስፒታሉ ለውጥ ያመጣበትና ለሌሎች የፊደራልና የክልል ሆስፒታሎችም እንደልምድ የሚወሰድ ተቋም መሆኑን ከጤና ሚኒስቴር የሜዲካል ሰርቪስ መሪ ስራ አስፈፃሚ ክፍል በእለቱ የተገኙት ሲ/ር እታፈራሁ አላማው ገልፀዋል፡፡
ሆስፒታሉ በቅርብ ጊዜ የተሰጠውን የካይዘን ትግበራ እየተጠቀመበትና ለውጥ እያመጣበት ለሌሎችም ተቋማት ተሞክሮ ሆኖ ስለተገኘ እኛም ከሆስፒታሉ ጎን በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ የሚደግፉ መሆኑንም የጃፓን አለም አቀፍ ትብብር ድርጅትና የካይዘን የልዕቀት ማዕከል ተወካዮች የገለፁ ሲሆን ካይዘን ተግባረዊ የሆነባቸውን የስራ ክፍሎችን ተዘዋውረው ጉብኝት አድርገዋል፡፡

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved