ሆስፒታሉ ከኢትዮጵያ ቀዶ ህክምና ማህበር ፕሬዘዳንትና ኮሴክሳ ከፍተኛ የክርስታልና የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት፡፡ 

News Image
በኢትዮጵያ ካሉ አንጋፋ ሆስፒታሎች መካከል አንዱ የሆነው አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በዓለም አቀፍ ለ23ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ከአስርት አመታት በኋላ ለ2ኛ ጊዜ የተከበረውን ከ14 የአፍሪካ ሃገራት በላይ መስራት የሚያስችለውን አለም አቀፍ የቀዶ ህክምና የብቃት ማረጋገጫ /ኮሴክሳ /The callege of surgeons of East, central, and southern Africa(COSECSA) ፈተና በጥሩና በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁ ይታወቃል፡፡
በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው 23ኛው የኮሴክሳ አለም አቀፍ ሳይንትፊክ ኮንፍረንስ የኮሴክሳ ሰርጅን ኮሌጅ ያዘጋጀውን ፈተና ወስደው ያለፉ ከ 152 በላይ የተለያዩ ሰርጅን ባለሙያዎች ምርቃት ተከናውኖላቸዋል።
ይህንን አለም ዓቀፍ ፈተና እና ኮንፈረንስ የተሳካ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከተው አለርት ሆስፒታል የክርስታልና የእውቅና ምስጋና ምስክር ወረቀት ከኢትዮጵያ ቀዶ ህክምና ማህበር ፕሬዘዳንት የተበረከተለት ሲሆን ሆስፒታሉ በተለያዩ ጊዜያት በሚያከናውናቸው አለም አቀፍና ሃገር ዓቀፍ ዝግጅቶች ላይ ምስጋናዎች እየተቸሩት ይገኛል፡፡

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved