ከ200 በላይ ለሚሆኑ የመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር አባላት ነፃ የህክምና አገልግሎት ተሰጠ፡፡

News Image
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ደከመኝ ሰለቸኝ የማይሉ የህክምና ባለሙያዎችን ይዞ ከመደበኛው የህክምና አገልግሎት በተጨማሪ በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት የሚሰጠውን ተከታታይ የሆነ ነፃ የበጎ አድራጎት የህክምና አገልግሎቱን ቀጥሎበታል፡፡ ሆስፒታሉ ነፃ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ የበጎ አድራጎት ህክምና ቡድን በማቋቋም ለተለያዩ የማህበረሰብ አካላት እየሰጠ በሚገኘው የመልካምነት ስራ ላይ ከፊደራል ሆስፒታሎች በቀዳሚነት ደረጃ ላይ እያስቀመጠውም ይገኛል፡፡ ለዚህም የተለያዩ የምስጋና እና የእውቅና ምስክር ወረቀቶች እየተበረከተለት ነው፡፡ የህክምና ቡድኑ በዛሬው እለት ከ7 ሺ በላይ የማህበረሰብ አካላት በሚኖሩበት መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር ነፃ የህክምና አገልግሎት የሰጠ ሲሆን በቆዳ ህክምና፣በዓይን ህክምና፣በአጥንት ህክምና ፣በውስጥ ደዌ ህክምና እና በነርብ ህክምና ላይ ችግር ያለባቸውን አረጋውያን ማህበረሰቦችን ማገልገል ተችሏል፡፡ ነፃ የህክምና አገልግሎት የበጎ አድራጎት ስራው በሆስፒታሉ ህክምና ቡድን ከመደበኛ የህክምና አገልግሎቱ በተጨማሪ ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው በሚለው መርህ ቀጣይነት ያለው ስራ እንደሚሰራም የሆስፒታሉ የህክምና ባለሙያዎች ገልፀዋል፡፡
News ImageNews ImageNews ImageNews ImageNews Image

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved