የሆስፒታሉን የመሰረተ ልማት የስራ አፈፃፅም የተከበሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጉብኝት አደረጉ፡፡

News Image
ህዳር 24/2016 ዓ/ም የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላትና የጤና ሚኒስቴር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰን ጨምሮ የተለያዩ ሚኒስቴር ዴኤታዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በተቋሙ እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ-ልማትና ሆስፒታል አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮጀክቶችን አፈፃፅምና የህሙማን አገልግሎት አሰጣጥን ተዘዋውረው ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ ላይ በአዲስ የተደራጁ የድንገተኛ አደጋና የጥርስ ህክምና ክፍል ጨምሮ በሆስፒታሉ ለታካሚ ምቹ የሆኑ የመሰረተ ልማት ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን ጉብኝቱ ለተቋሙ ሰራተኞች ተነሳሽነትን የሚፈጥርና በሚሰጡ ግብረ መልሶችም የማሻሻያ እርምጃዎችን ለመውሰድ እንደሚያስችል ተገልጿል።
በጉብኝቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶና እና ሌሎች የምክር ቤት አባላትም ተገኝተውበታል።

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved