የሆስፒታል ቱሪዝም መስህብነትን ለመጨመር በጎ ተጽእኖ የሚኖረው የኮሴክሳ አለማቀፍ ፈተና በነገው እለት ይጀመራል፡፡

News Image
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አለማቀፍና ሃገር ዓቀፍ ግንኙነቶችን በማጠናከር ታላላቅ ክንውኖችን ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡
በሆስፒታላችን የፊታችን ሰኞ ሁለት ዋና ዋና አለማቀፍና ሃገር ዓቀፍ ዝግጅቶች የሚከናወኑ ሲሆን የመጀመሪያው በ14 የአፍሪካ ሀገራት መስራት የሚያስችል የቀዶ ህክምና የብቃት ማረጋገጫ /ኮሴክሳ /ፈተና ይሰጣል፡፡
የቀዶ ህክምና የብቃት ማረጋገጫ ፈተናው ከ14 የአፍሪካ ሀገራት ለተውጣጡ ከ170 በላይ የህክምና ባለሙያዎች የሚሰጥ ሲሆን በዚህ ፈተና ላይ የምስራቅ፣ የደቡብና የመካከለኛው ምስራቅ አፍሪካ የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች ተሳታፊዎች ይሆናሉ፡፡
በሚሰጠው ፈተና ከሁሉም አህጉራት የተውጣጡ ከ300 በላይ ፕሮፌሰሮች በፈታኝነት ይገኛሉ። ይህ አለም ዓቀፍ ዝግጅት መከናወኑ ሆስፒታሉን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚደረገውን የእንቅስቃሴ ተግባር ውጤታማ የሚያደርግ ይሆናል፡፡ በዚህ ፕሮግራም ላይ የተለያዩ የፊደራል ሆስፒታል የስራ እንቅስቃሴዎች በኤግዚቪሽን ለታይታ ይቀርባሉ፡፡
በተጨማሪም በእለቱ ከ200 በላይ የተከበሩ የተወካዮች ምክርቤት አባላት በተቋሙ እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ-ልማትና ሆስፒታል አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮጀክቶችን አፈፃፅምና የህሙማን አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ጉብኝት ያደርጋሉ።
እነዚህ ታላላቅ ሁነቶች በሆስፒታሉ መከናወናቸው ለተቋሙም ሆነ እንደ ሃገር ለጤና አገልግሎቱ መሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል።
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከዘጠኝ አስርት አመታት በላይ ለተገልጋዩ ማህበረሰብ አንጋፋና አንቱ በተባሉ ህክምና ባለሙያዎች አገልግሎቱን እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታታሪና ብቁ አመራሮችን ይዞ አለም ዓቀፍና ሃገራቀፍ ግንኙነቶችን እያሰፋና እያጠናከረ ቀጥሏል፡፡

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved