በሆስፒታሉ ሲሰጥ የነበረው አለም አቀፍ የቀዶ ህክምና የብቃት ማረጋገጫ /ኮሴክሳ /ፈተና ተጠናቀቀ፡፡ 

News Image
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአለምአቀፍ ደረጃ ለ23ኛ ጊዜ እንደ ኢትዮጵያ ደግሞ ከአስር አመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኘውን አለምአቀፉን የቀዶ ህክምና የብቃት ማረጋገጫ/ኮሴክሳ/ፈተና እንዲያስተናግድ በሃገር አቀፍ ደረጃ ተመርጧል፡፡
ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የቀዶ ህክምና የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ከ14 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የህክምና ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህ ፈተና ላይ በጠቅላላ ቀዶ ህክምና 100 ፈታኞችና 60 ተፈታኞች፣በአጥንት ቀዶ ህክምና 57 ፈታኞችና 43 ተፈታኞች እንዲሁም ከፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ 17 ተፈታኝ እና 29 ፈታኞች በጥቅሉ ከ120 በላይ ተፈታኞች ተገኝተውበታል፡፡
በፈተናው ላይ የምስራቅ፣ የደቡብና የመካከለኛው ምስራቅ አፍሪካ የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች ተሳታፊዎች በመሆን ከሁሉም አህጉራት የተውጣጡ ከ186 በላይ ፈታኝ ፕሮፌሰሮች በፈታኝነት የተገኙ ሲሆን ከ50 በላይ እንግዳ ተቀባዮችና አስተባባሪ ኮሚቴዎች ተሳትፈውበታል፡፡
ይህ አለም ዓቀፍ ፈተና በተቋሙ በሚሰጥበት ጊዜ ለሆስፒታሉም ሆነ ለባለሙያው ትልቅ ልምድና ተሞክሮ የሚሆን ነው፡፡
ከተለያዩ ፈታኞችና ተፈታኞች ለሆስፒታሉ በተሰጠው ግብረ መልስ መሰረት ከዚህ በፊት ከነበረው የተሻለና ለወደፊትም ለሌሎች ሃገራትም የልምድ ልውውጥ የሚደረግበት ሆስፒታል እንደሚሆንም አስተያይታቸውን ሰጠዋል፡፡
በሆስፒታሉ የተካሄደው አለማቀፍ ፈተና በጥሩና በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀ በመሆኑ ለዚህ ፕሮግራም ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ሆስፒታሉ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved