ሆስፒታሉ በተለያዩ የመንግስትና የግል ድርጅቶች የሚሰጠውን ነፃ የበጎ አድራጎት የስራ እንቅስቃሴ መስራቱን ቀጥሏል፡፡

News Image
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታህሳስ 2/2016 ዓ.ም በውድ አረጋውያን በጎ አድራጎት ማህበር በመገኘት በሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት የሆስፒታሉን የህክምና ቡድን በመያዝ ከ100 በላይ የአረጋውያን ማህበር አባላትን ነፃ ህክምና አገልግሎት ሰጠዋል፡፡
በእለቱ አለም አቀፍ የአረጋውያንና የፆታዊ ጥቃት ቀንን ምክንያት በማድረግ ሆስፒታሉ የድፎ ዳቦና የውሃ ስጦታዎችን ያደረገ ሲሆን አለርት ሆስፒታል ከውድ አረጋውያን ማህበር ጎን በመቆም እስካሁን ላደረገውና እያደረገ ላለው የበጎ አድራጎት ስራ ከማህበሩ የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶለታል፡፡
የበጎ አድራጎት የእንቅስቃሴ ስራዎች ከመደበኛ ስራዎች በተጨማሪ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved