ሆስፒታሉ በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መጎብኘቱን ቀጥሏል፡፡

News Image
ታህሳስ 4/2016 ዓ.ም የፊደራል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሰራተኞች የአንጋፋውን አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተለያዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎችን ተዘዋውረው በመጎብኘት ታካሚዎችን ጠይቀዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሽመልስ ገዛኸኝ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ለእንግዶች ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸው ሆስፒታሉ ከ34 ሄክታር መሬት በላይ ያረፈና ከዘጠኝ አስርት አመታት በላይ ያስቆጠረ ታሪካዊ የህክምና ማዕከል እንደሆነ ገለፃ አድርገዋል፡፡
በዚህም ሆስፒታሉ በምርምር፣ አለማቀፍና ሃገር አቀፍ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የሆስፒታል አገልግሎት ስራዎችን አንጋፋ በሆኑ የህክምና ባለሙያዎች ለተገልጋዩ ማህበረሰብ አገልግሎቱን ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝና ሆስፒታሉን ከሌሎች ሆስፒታሎች በተለየ መልኩ ከስጋዊ ህክምና በተጨማሪ መንፈሳዊ ህክምናዎችን በማጠናከር የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት አባቶች ታካሚዎችን ጉብኝት ማድረጋቸውና ለህሙማኑም ሆነ ለባለሙያዎች የስራ ተነሳሽነትን እና ብርታትን የፈጠረላቸው መሆኑን ጠቁመው ታካሚን መጠየቅ ክብር በመሆኑ እናንተም አክብራችሁን ስለመጣችሁ ምስጋና ይገባችኋል ሲሉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
በእለቱ ዋርድ 4፣ የስነ- አዕምሮ ህክምናና ምርምር አገልግሎት ክፍል፣መድሃኒቱን የተለማመደ ቲቢ ህክምና ክፍል፣የጥርስ፣የመንጋጋ፣የአፍና የፊት ቀዶ ጥገና ህክምና ክፍሎችን ጨምሮ ሆስፒታሉ የህክምና ቱሪዝም ለማድረግ በቅርስነት ያስመዘገበውን የመጀመሪያውን ሆስፒታል ጉብኝት ተደርጎባቸዋል፡፡
በተመሳሳይ የአርማወር ሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩትን አዲሱን ህንፃ የጎበኙ ሲሆኑ የምርምር ኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ የአለርት ሆስፒታል መፈጠር በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያና የተለየ የምርምር ማዕከል እንዲመሰረት አድርጓል፡፡ ለዚህም አለርት ሆስፒታል ቀደምትና ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ ያለና በተለያዩ ሃገር አቀፍና አለምአቀፍ ተቋማት ዘንድ እውቅናው እየጨመረ መሄዱን ገልፀዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ ከተገኙት አቶ ደስታው ብዙአየሁ የፊደራል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የቢሮ ሃላፊ ናቸው፡፡ እሳቸው እንደሚሉት የሆስፒታሉን ታካሚዎች መጠየቃችን ተቋሙን የበለጠ ያወቅንበትና ብዙ ልምዶችን ያገኘንበት በመሆኑ በሌሎች ሆስፒታሎችም በተመሳሳይ ደረጃ እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል፡፡
ወ/ሪት አዳነች በዳዳ ሌላኛዋ አስተያይት ሰጪ ሲሆኑ እንደ ሃገር ሆስፒታሉ እየሰጠው ያለው አገልግሎት የሚበረታታ ነው፡፡ የተቋማችን ሰራተኞች ታካሚዎችን በመጠየቃችን እየተሰጠ ያለውን ህክምና አገልግሎት ከሚጠበቀው በላይ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ሆስፒታሉ አገልግሎት የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን ለጎብኝዎች፣ለታካሚዎችና ለሰራተኞችም ጭምር መንፈሳቸውን የሚያድሱበት ለእይታ ውብና ማራኪ የሆነ ነፋሻማ ተቋም መሆኑም አስደስቶናል ሲሉ አስተያይታቸውን ሰጠዋል፡፡

Contact Info

  1. +251 113 48 60 51 (Chief Executive Direcor)
  2. +251 113 47 16 32 (Chief Clinical Director)
  3. +251 113 48 11 63 (Chief Academic Director)
  4. hospital@alertcsh.org
  5. Zenebework, Kolfe Keranyo Addis Ababa, Ethiopia

Find Us On

  • Copyright © 2023 Alert Comprehensive Specialized Hospital. All Right Reserved